2015 ኤፕሪል 6, ሰኞ

የአማርኛ ተማሪዎች እርስ በርስ ዉይይት

የአማርኛ ተማሪዎች እርስ በርስ ዉይይት
የ3 ዓመት የአማርኛ ተማሪዎች እሁድ መጋቢት 27 ቀን 2007 ዓ.ም በመማሪያ ክፍላቸዉ ዉስጥ በመሰባብሰብ በአንዳንድ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ዉይይት አድርገዋል። በዉይይቱ ላይም የተለያዩ ሀሳቦች እና ጥያቄዎች ተነስተዉ ዉይይት ተደርጎባቸዋል። የዉይይቱ አጠቃላይ ሁኔታ በቪዲዮ የሚከተለዉን ይመስል ነበር።
            
                                              

2015 ማርች 24, ማክሰኞ

criticism

የስነ ምግባራዊ ሂስ ትንተና
መግቢያ
ስነ ምግባራዊ ሂስ በማህበረሰቡ ዘብድ ያሉ ባህላዊና ሀይማኖታዊ የስነምግባር መርሆኦችን መሰረት በማድረግ በአንድ የስነ ጽሑፍ ስራ ላይ የሚደረግ ምዘና ነዉ። በዚህ ሂስ ሀያሲዉ የቀረበዉ ስነ ጽሁፍ ምን ያህል ስነ ምግባርን ሊያስተምር እንደሚችል ይፈትሻል።  በዚህ አጭር ጽሁፍም ስነ ምግባራዊ ሂስ ምን እንደሚመስል እርቂሁን በላይነህ በ2000 ዓ.ም ያልተጠቡ ጡቶችና ሌሎችም በሚለዉ የአጭር ልቦለድ መድብል ዉስጥ በካራን የተገኘ መሲህ በሚል ርዕስ ያቀረበዉን ልቦለድ በተግባር ለመፈተሽ ሙከራ ይደረጋል።

የልቦለዱ አጽመ ታሪክ
አንድ ማርታ የምትባል ልጅ በካራን ትኖር ነበር። ማርታ አባቷ በህፃንነቷ ስለሞተባት እናትም አባትም ሆና ያሳደገቻት እናቷ ናት። የማርታ እናት ማርታን አሳድጋ አስተምራ  በአንድ መስሪያ ቤት በጸሀፊነት ተቀጥራ እያለች ታመመች። ማርታም ለእናቷ ማሳከሚያ የሚሆን 20 ሺህ ብር ተጠየቀች። ይህን የህክምና ወጭ ከፍላ የእናቷን ህይወት ከሞት ለመታደግ ያላደረገችዉ የለም። እናቷን ለማስታመም ከስራ ስለምጥቀር ከስራዋ ተባረረች፤ ገንዘብ አገኝበታለሁ ብላ ያመነችበትን ተግባር ሁሉ መፈጸም ጀመረች። አስርቱ ትዕዛዛትን ተላለፈች። በሴተኛ አዳሪነት በመሰማራት የእናቷን ህይወት ለማትረፍ ስትል አታመንዝር የሚለዉን ህግ ተላለፈች። በወንዶች ዘንድ ተወዳጅነትን ለማትረፍ ስትል ድንግልና አለኝ በማለት መዋሸት ጀመረች። አይኗን ጭቃ በመቀባትና በመሸፈን ማየት የተሳነኝ በማለት መለመን ጀመረች። ገንዘብ አለዉ ያሰበችዉን ሰዉ ለመዝረፍ ስትል ነፍስ አጠፋች። በመጨረሻም ይህን ሁሉ አድርጋ ሳይሳካላት ቢቀር ፈጣሪዋን በመካድና በፈጣሪዋ ተስፋ በመቁረጥ ወደ ደብተራ (ጠንቋይ) ዘንድ በመሔድ አጋንንት አስጎተተች መጽሐፍ አስገለጠች።

ማርታ ይህን ሁሉ አድርጋ እናቷን ከህመም መፈወስ አልቻለችም። በዚህ ሁኔታ አዝና ተክዛ እንደተቀመጠች ድንገት አማላክ በዐይነ ስጋ ተገልጦ አታቀርቅሪ ይላታል። ማርታ ግን አምላክነቱን አልተቀበለችም። ምክናያቱም አምላኳን ደጋግማ ለምና እናቷ ከህመሟ መፈወስ አልቻለችምና ነዉ። እኔ አምላክ ነኝ ሲላት አይደለህም ትለዋለች፤ ትሰድበዋለች፤ ታንጓጥጠዋለች፤ ትሳለቅበታለች። አምላክ አይደለህም አንተን የሩቁን ጩኸታችንን የማትሰማንን አምላክ ከምናመልክ ይልቅ የቅርቡን የምንዳስሰዉን የምንጨብጠዉን ደንጋዩን ብናመልክ የተሻለ ነዉ በማለት ትጮህበታለች። ከዚያም አምላኳን ትታ ደብተራዉ በነገራት መሰረት እናቷን መድሀኒት ስታጥናት አንድ ጊዜ ድምጽ አሰምታ ፀጥ ትልባታለች። መሲሁንም አንተ ቀናተኛ አምላክ አጋንንት አስጎትቼ መጽሐፍ አስገልጬ አንደበቷን ባስከፍተዉ መልሰህ ዘጋኸዉ በማለት ለፈለፈችበት። መሲሁም አሰርቱ ትዕዛዛቴን አላከበራችሁልኝም፤ በእጄ የፈጠርኳችሁ ፍጡሮቼ አምፃችሁብኛል፤ እያለ ማርታም አምላክ አይደለህም እያለች ስትሳለቅበት ከቆየች በኋላ አምላክ ከሆንክና ስልጣን ካለህ ስልጣንክን በተግባር አሳየኝ ከዚያም አምንሀለሁ አመልክሀለሁ አመሰግንሀለሁ ትለዋለች። ወዲያዉኑ መሲሁ እንግዲያዉስ የልብሽ ይሙላ በማለት ለዓመታት በህመም ስትሰቃይ የኖረችዉን የማርታን እናት ከህመም ፈወሰ፤ ማርታም አምላክነቱን በሚገባ አረጋገጠች፤ ማምስገንም ጀመረች።

በካራን የተገኘዉ መሲህ ከስነ ምግባራዊ ሂስ አንፃር
በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በርካታ ሀይማኖታዊ መርሆዎች አሉ። ለምሳሌ አስርቱ ትዕዛዛት ተብለዉ ከሚታወቁት መካከል፦ አታመንዝር፣ አትስረቅ፣ አትዋሽ፣ አትግደል፣ ከአምላክህ በቀር ሌላ አምላክ አታምልክ የሚሉት ይገኙበታል። የዕምነቱ ተከታዮችም እነዚህን ሀይማኖታዊ ህግጋት ለመፈፀም ይጥራሉ። በዕርቅ ይሁን በላይነህ በተጸፈዉ ያልተጠቡ ጡቶች በሚለዉ የአጭር ልቦለድ መድብል ዉስጥ ካሉት ልቦለዶች መካከል በካራን የተገኘዉ መሲህ በሚለዉ አጭር ልቦለድ ዉስጥ በርካታ ሀይማኖታዊና መጽሐፍ ቅዱሳዊ ጉዳዮች ተንፀባርቀዋል። የልቦለዱ ዋና ገጸባህሪ ማርታ በልቦለዱ ታሪክ ዉስጥ በተደጋጋሚ የእምነቱ ተከታዮች አጠንክረዉ የሚጠብቋቸዉንና የሚያከብሯቸዉን መጽሐፍ ቅዱሳዊ ስትተላለፍ ትስተዋላለች።ሆኖም ግን ደራሲዉ ከስነምግባር አንፃር ማስተላለፍ የፈለገዉ አንባቢዎች ለእናት ያላቸዉ ፍቅር እንዲጨምርና ሀይማኖታቸዉ በሚያዝዘዉ መልኩ ስነምግባራቸዉን ማነጽ እንደሚገባቸዉ ነዉ፡፡
ገጸ ባህሪዋ በርካታ ስነምግባር የጎደለዉ ድርጊት ስትፈጽም ትታያለች። ሆኖም ግን ይህ አይነት ስነ ምግባር የትም ሊያደርስ እንደማይችል በታሪኩ መጨረሻ ላይ በግልጽ ተቀምጧል። መዋሸት፣ አመንዝራነት፣ መግደል፣ በዛር በጠንቋይ ማምለክ ለዉርደት ለዉድቀት የሚዳርግ እንጂ የትም ሊያደርስ እንደማይችል ተገልጿል። ከታሪኩ ላይ እንደምንረዳዉ ማርታ የእናቷን ህመም በህክምና ለመከታተል ስትል በርካታ ትዕዛዛትን ተላልፋለች። ሆኖም በአንዱም ሲሳካላት አትስተዋልም። ዋሽታም፣ አመንዝራም፣ ነፍስ አጥፍታም ብር ልታገኝ አልቻለችም። የእናቷን ህመምም ማስታገስ አልቻለችም። በመጠኑም ቢሆን ትንሽ የተስፋ ጭላንጭልን ያሳያት የደብተራዉ ሙከራም ለደቂቃ የማይቆይ ተስፋ ሆነባት። ሙከራዋ ሁሉ ባዶ ሆነ። ደራሲዉ ገጸባህሪዋን በዚህ መልኩ ያቀረባትም ሆን ብሎ ይህ አይነት ስነምግባር የትም ሊያደርስ እንደማይችል ለአንባቢያን ለማስወቅ ካለዉ ፍላጎት የተነሳ  ነዉ። የአምላክን ትዕዛዝ ረስቶ ለአዋይ ለጠንቋይ ተገዝቶ እንኳንስ ከህመም መፈወስ አንድ ስንዝር እንኳ መራመድ የማይቻል መሆኑን ታሪኩ ይስገነዝባል። ልቦለዱም ይህ አይነት ስነ ምግባር ማለትም አምላክን የመካድ፣ ትዕዛዛትን ያለመፈፀም ወዘተ በማህበረሰቡ ዘንድ እንዳይከሰት ለማስገንዘብ ያለዉ አስተዋፅኦ ከፍተኛ ነዉ።

ማጠቃለያ
በአጠቃላይ በካራን የተገኘ ዉመሲህ ከስነ ምግባራዊ ሂስ አንፃር ሲታይ አንባቢዎችን ጥሩ ስነምግባር ሊያስተምር የሚችል ነዉ። ከማህበረሰቡ ባህላዊ የስነምግባር መርህ አንፃር ሲታይ ዋናዋ ገጸ ባህሪ ለእናቷ የምታደርገዉ በጎ ስራና የምትከፍለዉ መስዋትነት በማህበረሰቡ ዘንድ ተቀባይነት ያለዉና ሊበረታታ የኒገባዉ ስነምግባር ነዉ። ከሀይማኖት አንፃር ደግሞ ሁሉም ነገር ያለ አምላክ ፈቃድ ሊሆን እንደማይችል ያሳያል። ስለሆነም በአምላክ ማመን እንደሚገባ ያስተምራል።